👤👤Staff
Home About Us Main point Service Job Vacancy Materials Comment

"Please wait"
እባክወ በትዕግስት ይጠብቁ!

የጋዞ ወረዳ ከተማና መሰረተ ልማት ፅ/ቤት በመሰረተ ልማት ዙሪያ ከቦያ ከተማ ህብረተሰብ ጋር ውይይት አካሂዷል።ህዳር 16/2015 ዓ.ም

15-05-2026 14:52pm

በውይቱ ላይ የተገኘው የከተማው ህዝብ፣ የቀበሌው አመራርና የታዳጊው ከተማው ስራ አስኪጅና ባለሙያዎች በተገኙበት #ከተማውን ለማሳደግ የህብረተሰብ ተሳትፎወሳኝ በመሆኑ በጥሬ ገንዘብ፣ በጉልበትና በቁሳቁስ በመሰብሰብ ከተማውን ለማልማት ከህብረተሰቡ ጋር በመግባባት በጥሬ ገንዘብ ሰብስቦ አንድ ትራንስፎርመር ለማስገባት መግባባት ላይ ተደርሷል። #በከተማው ውስጥ ሰነድ አልባ የሆኑ ቦታዎችን በአጭር ቀን ውስጥ ለማጠናቀቅ መግባባት ላይ የተደረሰ ሲሆን ይህ ወርሃዊ ስብሰባም በየወሩ እንደሚቀጥል መግባባት ላይ ተድርሷል። የጋዞ ወረዳ ከተማና መሰረተ ልመት ፅ/ቤት ኃላፊ የሆኑት አቶ አዳነ ታደሰ እንደገለፁት ከተማዋን ፅዱና ማራኪ ለማድረግ የከተማው ነዋሪ ያለ ማንም አስገዳጅነት ሁሉም የህብረተሰብ ክፍል በነቂስ በመውጣት ማፅዳት እንዳለበት አሳስበዋል።

loading

ይህ መረጃ 38 ጊዜ በተለያዩ ሰዎች ታይቷል ---) (----

   ይህንን መረጃ ከታች ባሉት 👇    👇    👇   ሚዲያወች በመጫን Share..

Comment Form